ለመራጭነት መመዝገቢያ መስፈርቶች
አንድ መራጭ በመራጭነት ተሳትፎ የሚፈልገውን ፓርቲ ወይም እጩ ተወዳዳሪ ለመምረጥ የሚችለው በቅድሚያ በመራጭነት ሲመዘገብ ብቻ ነው፡፡
- ኢትዮጵያዊ ዜጋ የሆነ
- በምዝገባው እለት እድሜው 18 ዓመትና ከዚያ በላይ የሆነ
- ለምዝገባ በቀረበበት የምርጫ ክልል ቢያንስ ለ6 ወራት የኖረ
ከላይ በዝርዝር የተቀመጠው እንደተጠበቀ ሆኖ በአዕምሮ ሕመም ምክንያት የመወሰን አቅም የሌለው መሆኑ ሥልጣን ባለው አካል ወይም በበቂ ማስረጃ የተረጋገጠበት ሰው እንዲሁም የመምረጥ መብቱ በሕግ ወይም አግባብ ባለው ሕግ መሠረት በፍርድ ቤት ውሳኔ የተገደበበት ሰው በመራጭነት ሊመዘገቡ አይችሉም፡፡
ምንጭ፡- የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ
ቅጽ 3 ቁጥር 125 መጋቢት 18 2013