የአፄ ኃይለ ሥላሴ ኃውልት የካቲት 3 ይመረቃል

0
556

በአፍሪከ ኅብረት ቅጥር ግቢ የቆመው የቀዳማዊ አፄ ኃይለ ሥላሴ ኃውልት የኅብረቱ መሪዎች ኃይለሥላሴ ለአፍሪካ አንድነት ድርጅት መመስረት ላበረከቱት አስተዋጽኦ ኃውልት እንዲቆምላቸው በወሰኑት መሰረት የተሰራ ነው።

የውጭ ጉዳይ ሚንስቴር እንዳለው ኃውልቱ የመሪዎቹ ጉባኤ በሚካሄድበት ዕለት የካቲት 3/2011 በይፋ ይመረቃል።
በጉባኤው ኢትዮጵያዊያንና አፍሪካዊያን አርቲስቶች የሚካፈሉበት የሙዚቃ ዝግጅት ይካሄዳል።

መጪው 32ኛ የአፍሪካ ኅብረት የመሪዎች ጉባኤ በተለያዩ ደረጃዎች በሚካሔዱ ስብሰባዎች ከጥር 30 እስከ የካቲት 4 የሚቆይ ነው።

ቅጽ 1 ቁጥር 12 ጥር 25 ቀን 2011

መልስ አስቀምጡ

Please enter your comment!
Please enter your name here