ፕሬዚዳንት ሣህለ ወርቅ ዘውዴ “ሮድ ቱ አዲስ ፓርትነር ቱ ኮኔክት” በተሰኘው ዓለም ዐቀፍ ጉባኤ ላይ በበይነ መረብ በመታገዝ የቪድዮ መልዕክትን አስተላለፉ፡፡
ፕሬዚዳንቷ ለጉባዔው ባስተላለፉት መልዕክት በቴሌኮም ዘርፍ ውስጥ ባለድርሻ አካላት ፣ ባለሀብቶች እና ሽርክናዎች በጋራ በመሆንና ሀብትን በማቀናጀት መረጃ ልውውጥንም ሆነ የዲጂታል ቴክኒዮሎጂን ለማስፋፈት መጣር ይገባቸዋል ብለዋል።
በፈረንጆቹ ሰኔ 2022 የዓለም አቀፍ የቴሌኮሚኒኬሽን ህብረት የዙር ጉባዔ አዲስ አበባ ውስጥ እንደሚካሄድም ከፕሬዝዳንት ጽሕፈት ቤት ያገኘነው መረጃ አመላክቷል።