ምክር ቤቱ የጥላቻ ንግግርና የሀሰተኛ መረጃ ስርጭት አዋጅን አፀደቀ
የኢፌዴሪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ የካቲት 5/2012 ባደረገው አስቸኳይ ጉባኤ የጥላቻ ንግግርና የሀሰተኛ መረጃ ስርጭትን ለመከላከልና ለመቆጣጠር የቀረበ አዋጅ አፀደቀ።
የህግ፣ ፍትህና ዴሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የጥላቻ ንግግርና የሃሰተኛ መረጃ ስርጭትን ለመከላከልና ለመቆጣጠር የቀረበ አዋጅን በተመለከተ ያቀረበውን ሪፖርትና የውሳኔ ሃሳብ ተመልክቶ አዋጁን በ23 ተቃውሞ እና በ2 ድምጸ ተአቅቦ እንዲሁም በአብላጫ ድምጽ አጽድቆታል።