በኦሮሚያ ልዩ ዞን በተከሰቱ ሁለት ድንገተኛ አደጋዎች ምክንያት የ8 ሰዎች ህይወት ማለፉ ተገለፀ

0
1302

ሰኞ ታህሳስ 18/ 2014 (አዲስ ማለዳ) ባለፉት ሁለት ቀናት በኦሮሚያ ልዩ ዞን በደረሱ ድንገተኛ አደጋዎች በድምሩ የስምንት ሰዎች ህይወት ማለፉን የአዲስ አበባ የእሳት እና የአደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አስታውቋል፡፡

በአለም ገና ዋስ ማደያ ጀርባ በህንጻ መደርመስ እንዲሁም በቀራኒዮ ጸበል ሰፍር አካባቢ በአንድ ግለሰብ መኖርያ ቤት በደረሰው የእሳት አደጋ ምክንያት አራት ህጻናት እና አባራው በአደጋው ምክንያት ህይወታቸው ማለፉን የእሳት እና የአደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን የህዝብ ግኑኝነት ሃላፊ ጉልላት ጌታነህ ለኢትዮ ኤፍ ኤም ተናግረዋል፡፡

በዚሁ አደጋ የተነሳ 200 ሺህ ብር የሚጠጋ ንብረት መውደሙን ተናግረው 2ሚሊየን ብር የሚጠጋ ንብረት ግን ማዳን ተችሏል ብለውናል፡፡

በአለም ገና በህንጻ መደርመስ አደጋ ደግሞ የሁለት ሴቶች እና የአንድ ወንድ ህይወት ማለፉንም ነው ጉልላት የተናገሩት፡፡

መልስ አስቀምጡ

Please enter your comment!
Please enter your name here