ከአልኮል ነፃ የሆነ አዲስ መጠጥ ለገበያ ቀረበ

0
1112

ሐበሻ ቢራ ፋብሪካ አክሲዮን ማኅበር ከአልኮል ነፃ ነው የተባለና ‹‹ንጉሥ›› የተሰኘ የማልት (ብቅል) መጠጥ አምርቶ ለገበያ ማቅረቡን አስታወቀ።

ንጉሥ የተሰኘው መጠጥ ከአልኮል ነፃ በመሆኑ ከለስላሳ መጠጦች ጋር እንደአማራጭ መቅረብ እንዲችል ሆኖ መዘጋጀቱን አክሲዮን ማኅበሩ አስታውቋል።

አምራች ድርጅቱ በላከው መግለጫ የአዲሱ ምርት አቅርቦት በመጀመሪያ በአዲስ አበባ እና ደብረ ብርሃን እንደሚሆን አመልክቷል።

‹‹ንጉሥ›› በማኅበረሱ ውስጥ ትልቅ ቦታ የሚሰጠው እና ስያሜውን ለማስታወስም ቀላል ሆኖ በመገኘቱ ለምርቱ መጠሪያ እንዲሆን መመረጡን ገልጿል።

የአክሲዮን ማኅበሩ መጀመሪያ ስምንት ሺህ በሚሆኑ ኢትዮጵያዊያን ባለአክስዮኖች የተቋቋመ ሲሆን ሽያጩንም በ2ዐዐ8 መጀመሩ ይታወሳል። የቢራ መጥመቂያ ፋብሪካውንም ደብረ ብርሃን ላይ ገንብቶ ወደ ሥራ ከገባ ዓመታት ተቆጥረዋል።

ቅጽ 1 ቁጥር 14 የካቲት 9 ቀን 2011

መልስ አስቀምጡ

Please enter your comment!
Please enter your name here