የፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት የልደታ ምድብ ችሎት የኢንፎርሜሽን መረብ ደኅንነት ኤጀንሲ ባልደረባ ለነበሩት ቢኒያም ተወልደ የዋስትና መብት መፍቀዱን ተከትሎ የዐቃቤ ሕግ የይግባኝ ሒደትን ለመጠባበቅ 10 ቀን ቀጠሮ ሰጠ።
ዛሬ፣ ሐምሌ 29/2011 ስምንት ሰዓት በዋለው ችሎት ፍርድ ቤቱ ተከሳሽ የዋስትና መብታቸው እንዲፈቀድ የበየነ ሲሆን ዐቃቤ ሕግም በፀረ ሙስና አዋጁ መሰረት ተከሳሽ የተከሰሱባቸው አራት ክሶች ሲደመሩ ከ10 ዓመት በላይ በመሆኑ የዋስትና መብት መፈቀዱ አግባብ አይደለም ሲል በጽሑፍ ተቃውሟል።
በሕጉ መሰረትም በውሳኔው ላይ ይግባኝ እላለሁ ያለው ዐቃቤ ሕግ ከፍርድ ቤቱ የውሳኔ ግልባጭ ለማውጣት እና ለጠቅላይ ፍርድ ቤት ይግባኝ ለማለት 10 ቀን የተፈቀደለት ሲሆን ተከሳሽም እስከ ቀጠሮ ቀኑ ድረስ በማረፊያ የሚቆዩ ይሆናል።