ማክሰኞ ሰኔ 21 ቀን 2014 (አዲስ ማለዳ) የቀድሞ የኢትዮ ፎረም አዘጋጅ ጋዜጠኛ ያየሰው ሽመልስ በድጋሚ መታሰሩን ጠበቃው ታደለ ገ/መድህን ገለፁ።
ጋዜጠኛው ዛሬ ማለዳ ላይ ከመኖሪያ ቤቱ ሲቪል በለበሱ የፀጥታ አካላት መወሰዱን ነው ጠበቃው የተናገሩት።
ጋዜጠኛ ያየሰው ሽመልስ ባሳለፍነው ሳምንት በፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት አራዳ ምድብ ጊዜ ቀጠሮ ችሎት በሰጠው የዋስትና መብት ከእስር መፈታቱ ይታወሳል።
ምንጭ፦ ጋዜጠኛ ታሪክ አዱኛ