ዘመነ ካሴ በሕግ ቁጥጥር ሥር መዋሉን የአማራ ክልል ፓሊስ ኮሚሽን አስታወቀ

0
1358

ዕረቡ መስከረም 11 ቀን 2015 (አዲስ ማለዳ) በአማራ ክልል ፓሊስ ኮሚሽን የታክቲክ ምርመራ ምክትል ዘርፍ ኃላፊ ኮማንደር ክንዱ ወንዴ በሰጡት መግለጫ፤ ዘመነ ካሴ በኅብረተሰቡ ጥቆማ በሕግ ቁጥጥር ሥር ውሎ ምርመራ እየተካሔደበት ነው ብለዋል።

በባሕር ዳር ከተማ ቀበሌ 03 ከግለሰብ ቤት መያዙን ገልጸዋል።የወንጀል ተጠርጣሪው በሕግ ቁጥጥር ሲውል 541 ሺህ ብር እና ከሌሎች ኤግዚቢቶች ጋር መያዙን ተናግረዋል።

ምርመራው የሚካሔደው በክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን መሆኑን ማረጋገጣቸውን አሚኮ ዘግቧል።

ኮማንደር ክንዱ ተጠርጣሪው በሕግ ሲፈለግ እንደቆየ ገልጸው እንዲያዝ ለተባበረው ማኅበረሰብ ምስጋና አቅርበዋል።

ማንም ከሕግ ማምለጥ እንደማይችል የተጠርጣሪው መያዝ ማሳያ ነው ብለዋል።

መልስ አስቀምጡ

Please enter your comment!
Please enter your name here