ኢትዮ ቴሌኮም አዲስ የአራተኛውን ትውልድ (4G) ብሮድባንድ ኢንተርኔት አገልግሎት ለመኖሪያ ቤት አቀረበ

0
1877

ኢትዮ ቴሌኮም አዳዲስ ቴክኖሎጂ በመጠቀም መደበኛ ኢንተርኔት ተደራሽ ባልሆነባቸው ቦታዎች ላይ በአማራጭነት አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችል የአራተኛውን ትውልድ (4G) ገመድ አልባ ብሮድባንድ ኢንተርኔት አገልግሎት ለመኖሪያ ቤት ማቅረቡን ገልጿል።
አገልግሎቱ ደንበኞች በመኖሪያ አካባቢያቸው 4ጂ የሞባይል ኔትወርክን በመጠቀም ከፍተኛ ፍጥነት ያለው የኢንተርኔት አገልግሎት በተመጣጣኝ ዋጋ በቤት ውስጥ ማግኘት የሚያስችል አማራጭ ነውም ተብሏል።
ተቋሙ በሙከራ ደረጃ በተወሰኑ የሽያጭ ማዕከሎች ከአገልግሎት መስጫ ቀፎ ጋር በተመጣጣኝ ዋጋ ማቅረብ መጀመሩንም ጨምሮ አሳዉቋል።
የ‹ፊክስድ› ብሮድባንድ በመኖሪያ ቤት እና በንግድ ተቋማት ባለበት እንደሚቀጥልም ነው ኢትዮ ቴሌኮም የገለጸው።
እንዲሁም፣ በዚህ አግልግሎት 70 ሺሕ ደንበኞችን በአጭር ጊዜ ለማፍራት ማቀዱንም አመላክቷል። በኢትዮጵያ 136 ከተሞች የአራተኛውን ትውልድ (4G) አገልግሎት ተጠቃሚዎች መሆናቸው ተጠቁሟል።


ቅጽ 4 ቁጥር 177 መጋቢት 17 2014

መልስ አስቀምጡ

Please enter your comment!
Please enter your name here