የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ባለፉት ዘጠኝ ወራት 4.8 ቢሊዮን ዶላር ከሐዋላ እና ከወጪ ንግድ ማስገባቱን የባንኩ ፕሬዝዳንት ባጫ ጊና ባንኩ የዘጠኝ ወር እቅድ አፈፃፀሙን በገመገመበት ወቅት ተናግረዋል። ባንኩ ባለፉት ዘጠኝ ወራት ውስጥ 52 ቢሊዮን ብር ጠቀማጭ ሒሳብ ማሰባሰቡን እና ይሄም አጠቃላይ ተቀማጭ ሒሳቡን ግማሽ ትሪሊዮን ብር እንዲያልፍ ማድረጉንም ተናግረዋል።
ባንኩ አዳዲስ 109 ቅርንጫፎችን መክፈቱን በመክፈት አጠቃላይ የቅርንጫፎቹን ቁጥር ወደ 1ሺሕ 396 ለማድረስ ችሏል።
ቅጽ 1 ቁጥር 25 ሚያዚያ 19 ቀን 2011