የገቢዎች ሚኒስቴር በስድስት ወራት ከ 127 ቢሊዮን ብር በላይ ሰበሰበ

0
417

የገቢዎች ሚኒስቴር ባለፉት ስድስት ወራት 125 ነጥብ 7 ቢሊየን ብር ገቢ ለመሰብሰብ አቅዶ 127 ነጥብ 5 ቢሊየን ብር መሰብሰቡን አስታወቀ። ገቢው ካለፈው በጀት ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር የ28 ነጥብ 9 ቢሊየን ብር ብልጫ እንዳለው ሚኒስትር መስሪያ ቤቱ አስታውቋል።

አፈጻጸሙ የዕቅዱን 101 በመቶ ሲሆን በስድስት ወራት ከተሰበሰበው ገቢ ውስጥ 58 በመቶ ከሀገር ውስጥ ሲሆን ቀሪው ደግሞ ከጉምሩክ ገቢ የ የተሰበሰበ ነው። ከህግ ማስከበር ጋር በተሰራ ስራም ባለፉት ስድስት ወራት ከድርጊታቸው ያልተቆጠቡና ሀሰተኛ ደረሰኝ በመጠቀም ግብይት የፈፀሙ ድርጅቶች በህግ ተጠያቂ እንዲሆኑ መደረጋቸውንም ታውቋል። በግብይት ወቅትም ደረሰኝ የማይቆርጡ ድርጅቶች ላይ ድንገተኛ ክትትል በማድረግ ተጠርጣሪዎች በህግ ቁጥጥር ስር ውለው መቀጣታቸው ተገልጿል።

በሌላ በኩል የጉምሩክ ኮሚሽን በህብረተሰቡ ትብብር በ6 ወራት ውስጥ ከ1.2 ቢሊዮን ብር በላይ የሚገመቱ የገቢና ወጪ ኮንትሮባንድ እቃዎችና ህገ-ወጥ ገንዘብ መያዙን ገልጿል። አደንዛዥ እፆች፣ የጦር መሣሪያዎች፣ ኤሌክትሮኒክስ፣ ምግብ ነክ ሸቀጣ ሸቀጦች፣ ተሸርካሪዎች፣ ወደ ሀገር እንዳይገቡ ክልከላ የተደረገባቸው ዕቃዎች በ6 ወራት ውስጥ የተያዙ ሲሆን በተመሳሳይ ጊዜ ውስጥም 48.8 ቢሊዮን ብር ለመሰብሰብ አቅዶ 54.08 ቢሊዮን ብር መሰብሰብ ችሏል።

ገቢውንም ለመሰብስብ ሚኒስጤሩ ሰራተኞች ስራቸውን በሃላፊነት መወጣት መቻላቸው እንዲሁም ግብር ከፋዩ ማህበረሰብ ግብሩን በወቅቱ እና በታማኝነት እንዲከፍል በትኩረት በመሰራቱ ነው ተብለዋል። ግብር ከፋዮቹ በወቅቱና በታማኝነት ግብራቸውን በመክፈል የዜግነት ግዴታቸውን እንዲወጡ ጥሪ ማቅረባቸውን ከገቢዎች ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።

መልስ አስቀምጡ

Please enter your comment!
Please enter your name here