ትችት የበዛባቸው እጩ ራሳቸውን ከፌደራል ዳኞች አስተዳደር ጉባኤ አባልነት አገለሉ

0
676

በመክር ቤት አባላት አጩነታቸው ላይ ጥያቄና ትችት የተሰነዘረባቸው የቀድሞ የሕግና ፍትሕ አስተዳደር ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ገ/እግዚአብሔር አርአያ ከፌደራል ዳኞች አስተዳደር ጉባኤ አባላት ከእጩነት ራሳቸውን አገለሉ።
የፍትሕ ስርአቱ በተጠናከረ መንገድ እንዲቀጥልና ከዚህ ቀደም የታዩ ክፍተቶችን ለማረም በሚል የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ለፌደራል ዳኞች ጉባኤ አባላት ጴጥሮስ ወ/ሰንበትን፣ ሰናይት አንዳርጌን እና ገ/እግዚአብሔር አርአያን በእጩነት አቅርቦ ነበር፡፡
ምክር ቤቱም የጴጥሮስ እና ሰናይትን አባልነት በአብላጫ ድምፅ አጽድቆ ገ/እግዚአብሔር ‹‹የሕግ ሙያ የሌላቸው እና ከዚህ ቀደም በነበሩበት ቋሚ ኮሚቴ ክፍተቶች እንደነበሩ›› በመጥቀስ እንደገና እንዲታዩ ሲል ጠይቋል፡፡
ገ/እግዚአብሔር የሕግና ፍትህ ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ሆነው ባገለገሉበት ወቅት የዳኞች የስነ ምግባርና የዜጎች የሰብኣዊ መብቶች ላይ በርካታ ችግሮች ነበሩ ያሉት የሕዝብ እንደራሴዎች በእጩው ተገቢነት ላይ ጥያቄዎችን ሰንዝረዋል።በምክር ቤቱ የተነሳው ሐሳብ እውነት መሆኑን የገለጹት ገ/እግዚአብሔር የፌዴራል ዳኞች አስተዳደር ጉባኤ አባል መሆን እንደማይፈልጉ ጠቅሰው ራሳቸውን ከእጩነት አግልለዋል፡፡ ምክር ቤቱም በገ/እግዚአብሔር ምትክ ሌላ እጩ እንደሚያቀርብ አሳውቋል፡፡

ቅጽ 1 ቁጥር 6 ታኅሣሥ 13 ቀን 2011

መልስ አስቀምጡ

Please enter your comment!
Please enter your name here