ፈሊንት ስቶን ሆምስ በታንዛንያ ዳሬ ሠላም 14 ሺሕ ካሬ ሜትር ላይ የሚያርፉ አራት አፓርትመንት ሕንፃዎችን ለመገንባት በአገሪቱ ከሚገኙ ባለሀብቶች ጋር ስምምነት ላይ መድረሱ ታውቃል።
ኢትዮጵያዊው የቤት አልሚ ድርጅት አሁን ላይ ግንባታውን ለመጀመር የሚስችለውን ንድፉን (ዲዛይን) አጠናቆ ለታንዛንያ ቤቶች ኮርፖሬሽን ሊያስርክብ መሆኑን የድርጅቱ ምክትል ሥራ አስከያጅ ብሩክ ሽመልስ ለአዲስ ማልዳ ገልጸዋል።
በተጨማሪም በታንዛንያ ካልሳሳ ግዛት በስድስት ሺሕ 600 ካሬ ሜትር ላይ የሚያርፉ አፓርትመንቶችን ለመገንባት ስምምንት ላይ ደርሷል።
ፍሊንት ስቶን ሆምስ ሪል ስቴት በፀደቀ ይሁኔ የተመሠረተ ሲሆን እስካሁን ከ20 ሺሕ በላይ ቪላና አፓርታማ ሰርቶ ለተጠቃሚዎች እንዳስረከበ መረጃዎች ያሳያሉ።
ቅጽ 1 ቁጥር 6 ታኅሣሥ 13 ቀን 2011