ጠ/ሚ/ሩ ድንገተኛ ጉብኝት ማድረጋቸውን እንደሚቀጥሉ ገለፁ

0
564

ትናንት አረብ ረፋድ የጠቅላይ ዐቃቤ ሕግና የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን መሥሪያ ቤቶችን በድንገት የጎበኙት ጠቅላይ ሚንስትር ዐብይ አህመድ (ዶ/ር) ድንገተኛ ጉብኝት ማድረጋቸውን እንደሚቀጥሉበት አስታወቁ።
በኹለቱ የፌደራል መስሪያ ቤቶች ድንገተኛ ጉብኝትን ያደረጉት የጠቅላይ ሚንስትሩ ዓላማም በኹለቱ ተቋማት ላይ የመሥሪያ ቦታን በማስተካከል ውጤታማነትንና አፈፃፀምን በማሳደግ ረገድ የተሰሩ ሥራዎች እንዳሉ ለመገምገም ነው ተብሏል።
ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) በቀጣም ይህን መሰሉን ተግባር እንደሚያስቀጥሉ የተገለጸ ሲሆን፣ ተቋማት በእቅዳችው መሰረት ሥራቸውን በአስፈላጊው ፍጥነትና ጥራት እያከናወኑ ስለመሆኑ ለመታዘብና አቅጣጫም ለመስጠት እንዲያስችላቸው መሆኑን የጠቅላይ ሚንስትር ጽሕፈት ቤት እወቁልኝ ብሏል።
ኢትዮጵየ ለረጅም ጊዜ ግጭት ውስጥ መቆየቷን የጠቀሱት ጠቅላይ ሚንስትሩ፣ አሁን ላይ የመንግሥት ዕይታ ተስተካክሎ የምጣኔ ሃብት ልማት ላይ በትኩረት የሚሰራበት ነውም ብለዋል።

ቅጽ 1 ቁጥር 8 ታኅሣሥ 27 ቀን 2011

መልስ አስቀምጡ

Please enter your comment!
Please enter your name here