የእነ በረከት ስምዖን የዋስትና ይፈቀድልን ጥያቄ ውድቅ ሆነ

0
301

በጥረት ኮርፖሬት ሀብት በማባከን ወንጀል ተጠርጥረው ጥር 15 በአማራ ክልል መንግሥት በቁጥጥር ስር የዋሉት በረከት ስምዖንና ታደሰ ካሳ ያቀረቡት የወስትና ጥያቄ ውድቅ ሆነ።

ትናንት በባሕር ዳርና አካባቢዋ ከፍተኛ ፍርድ ቤት 2ኛ ወንጀል ችሎት ቀርበው ጉዳያቸው መታየት ከጀመረው ኹለቱ ተጠርጣሪዎች ውስጥ በረከት በጥረት ኮርፖሬት ኩባያዎች ጠፍቷል ለተባለው ገንዘብ የዋስትና መብታቸው ተከብሮ በውጭ ሆነው እንዲከራከሩ ጠይቀዋል። በባሕር ዳር ለሕይወታቸው እንደሚሰጉና የጤና ችግርም ስላባቸው ጉዳያቸው አዲስ አበባ እንዲታይላቸው ፍርድ ቤቱን ጠይቀዋል። ታደሰም በተመሳሳይ ጉዳያቸው አዲስ አበባ እንዲታይና በዋስ ወጥተው በውጭ እንዲከራከሩ ጠይቀዋል። በመገናኛ ብዙኃን የሥም ማጥፋት ዘመቻ እየተፈጸመብን ነው ሲሉም ተጠርጣሪዎቹ አቤት ብለዋል።

ግለሰቦቹ የተጠረጠሩት በከፍተኛ ገንዘብ ነው ያለው አቃቤ ሕግ በበከሉሉ የቀደመ ሥልጣናቸውን ተጠቅመው መረጃ ይሰውሩብኝል በሚልም የዋስ መብት እነዳያገኙ ጠይቋል።

የዋስትና ጥያቄውን ወድቅ ያደረገው ፍርድ ቤቱ የ14 ቀናት የምርመራ ጊዜን በመፍቀድ ለየካቲት 1 ቀጠሮ ሰጥቷል።

ቅጽ 1 ቁጥር 11 ጥር 18 ቀን 2011

መልስ አስቀምጡ

Please enter your comment!
Please enter your name here